23 ነጥብ 1 ቢለየን ብር ለድጎማ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች ተከፈለ

 ለድጎማ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች 23 ነጥብ 1 ቢለየን ብር በላይ መከፈሉን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታውቋል።

ባለሥልጣኑ በ2016 በጀት ዓመት መጀመሪያ ሩብ ዓመት÷ለነዳጅ ኮንትሮባንድ ሽያጭ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን 65 በመቶ መቀነስ መቻሉን አስረድቷል።

ከተቀመጠው አሠራር ውጭ አገልግሎት በማይሰጡና ነዳጅ ሣይቀዱ የድጎማ ክፍያ ለሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች ትብብር በሚፈፅሙ 5 ነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ መውሰዱንም ጠቁሟል።

እስከ ባለፈው መስከረም ወር መጨረሻ ድረስም 23 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ ለድጎማ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች መከፈሉን የባለስልጣኑ መረጃ ያመላክታል።

በዚሁ መንገድ 120 ቢሊየን ብር በላይ ዋጋ ያለው የነዳጅ ግብይት የተፈጸመ ሲሆን÷የነዳጅ ስርጭት ቁጥጥርን ለማዘመን ነዳጅ ጫኝ ተሽከርካሪዎች ጂ ፒ ኤስ እንዲገጥሙ መደረጉ ተገልጿል።

ማደያ በሌለባቸው 556 ወረዳዎች አዳዲስ ማደያዎች እንዲገነቡ በተቀመጠው ዕቅድ መሰረትም በ8 ወረዳዎች አዳዲስ ማደያዎች ተገንበተው የነዳጅ ትስስር ፈቃድ ማግኘታቸው ተጠቅሷል።

ምንጭ፦ ኤፍ.ቢ.ሲ

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *