ኮሚሽኑ ባለፉት አራት ወራት 64 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ሰበሰበ

የጉምሩክ ኮሚሽን ባለፉት አራት ወራት 64 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 95 በመቶ ማሳካቱን አስታወቀ።

ኮሚሽኑ በአራት ወራት የተከናወኑ ሥራዎችን የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል።

በገቢ አሰባሰብ፣ ኮንትሮባንድ እና ሕገ- ወጥ ንግድን በመከላከል ረገድ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ናቸው መባሉን የኮሚሽኑ መረጃ አመላክቷል።

የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ÷ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይ ወራትም በበጀት ዓመቱ የተያዘውን የገቢ ዕቅድ ለማሳካት በሚያስችሉ ሥራዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ አመላክተዋል።

ምንጭ፦ ኤፍ.ቢ.

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *