![](https://onestopinvestmentservices.com/wp-content/uploads/2023/10/392939240_637717635211994_3231980289365092050_n-1.jpg)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም መክፈቻ መርሃ ግብር ላይ ንግግር አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የቻይና-አፍሪካን ግንኙነት ጥንተ መሰረት እና እድገት አውስተው በቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ (BRI) የመሰረተ ልማት ክንውን በአፍሪካ አህጉር የተጣለውን ጠንካራ የትብብር መሰረትም አንስተዋል።
![](https://onestopinvestmentservices.com/wp-content/uploads/2023/10/66-3-1-1024x576.png)
በማደግ ላይ ያለውን የአፍሪካን ተፅእኖ የመፍጠር አቅም አፅንዖት በመስጠትም በባለ ብዙ ወገን መድረኮች አካታችነትን ማረጋገጥ ተገቢ እንደሆነም አስረድተዋል።