የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮምሽን ከኢስት አፍሪካ ኢንደስትሪያል ፓርክ ጋር ተፈራረመ፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮምሽን ከኢስት አፍሪካ ኢንደስትሪያል ፓርክ ጋር ኢስት አፍሪካ ሆልዲንግ ኩባንያን ወደ ኢንደስትሪ ፓርክ ለማሳደግ የሚያስችለውን የአልሚነት ስምምነት ተፈራርሟል፡፡

በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ በ100.6 ሄክታር መሬት ላይ የሚለማው ኢስት አፍሪካ ኢንደትሪያል ፓርክ የተለያዩ ቅይጥ የአምራች ኢንደስትሪዎችን እንደሚያካትት የተገለፅ ሲሆን የስራ ዕድልን በመፍጠር፣ የክህሎት እና ቴክኖሎጂ ሽግግርን በማጎልበት እዲሁም ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመቀነስ እና ኤክስፖርትን በመጨመር የራሱን ጉልህ ድርሻ እንደሚወጣ በፊርማ ስነ ስርዕቱ ተጠቅሷል፡፡

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *